የሐዋርያው፡ጳውሎስ፡መልእክት፡
ወደቆላስይስ፡ሰዎች።

(ክለሳ.1.20020507)

_______________ቆላስይስ፥ምዕራፍ፡1።______________
ምዕራፍ፡1፤
1፤በእግዚአብሔር፡ፈቃድ፡የኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ሐዋርያ፡የኾነ፡ጳውሎስ፡ጢሞቴዎስም፡ወንድሙ፥
2፤በቆላስይስ፡ለሚኖሩ፡ቅዱሳንና፡በክርስቶስ፡ለታመኑ፡ወንድሞች፤ከእግዚአብሔር፡ከአባታችን፡ከጌታም፡ከኢየ ሱስ፡ክርስቶስ፡ጸጋና፡ሰላም፡ይኹን።
3-5፤ስለ፡እናንተ፡ስንጸልይ፥በሰማይ፡ከተዘጋጀላችኹ፡ተስፋ፡የተነሣ፡በክርስቶስ፡ኢየሱስ፡ስለ፡እምነታችኹ፡ ለቅዱሳንም፡ዅሉ፡ስላላችኹ፡ፍቅር፡ሰምተን፥የጌታችንን፡የኢየሱስ፡ክርስቶስን፡አባት፡እግዚአብሔርን፡ዅልጊ ዜ፡እናመሰግናለን፤ስለዚህም፡ተስፋ፡በወንጌል፡እውነት፡ቃል፡አስቀድማችኹ፡ሰማችኹ።
6፤ይህም፡በዓለም፡ዅሉ፡ደግሞ፡እንዳለ፡ወደ፡እናንተ፡ደርሷል፥የእግዚአብሔርንም፡ጸጋ፡በእውነት፡ከሰማችኹበ ትና፡ካወቃችኹበት፡ቀን፡ዠምሮ፥በእናንተ፡ደግሞ፡እንዳለ፡እንዲህ፡በዓለም፡ፍሬ፡ያፈራል፥ያድግማል።
7፤ከተወደደ፡ከእኛም፡ጋራ፡ዐብሮ፡ባሪያ፡ከኾነው፡ከኤጳፍራ፡እንዲህ፡ተማራችኹ፥ርሱም፡ስለ፡እናንተ፡ታማኝ፡ የክርስቶስ፡አገልጋይ፡ነው።
8፤ደግሞም፡በመንፈስ፡ስለሚኾን፡ስለ፡ፍቅራችኹ፡አስታወቀን።
9፤ስለዚሁ፡እኛ፡ደግሞ፡ይህን፡ከሰማንበት፡ቀን፡ዠምረን፡የፈቃዱ፡ዕውቀት፡መንፈሳዊ፡ጥበብንና፡አእምሮን፡ዅ ሉ፡እንዲሞላባችኹ፡እየለመንን፥ስለ፡እናንተ፡ጸሎትን፡አልተውንም።
10-11፤በበጎ፡ሥራ፡ዅሉ፡ፍሬ፡እያፈራችኹ፡በእግዚአብሔርም፡ዕውቀት፡እያደጋችኹ፥
12፤ከደስታም፡ጋራ፡በዅሉ፡ለመጽናትና፡ለመታገሥ፡እንደ፡ክብሩ፡ጕልበት፡መጠን፡በኀይል፡ዅሉ፡እየበረታችኹ፥ በቅዱሳንም፡ርስት፡በብርሃን፡እንድንካፈል፡ያበቃንን፡አብን፡እያመሰገናችኹ፥በነገር፡ዅሉ፡ደስ፡ልታሠኙ፡ለ ጌታ፡እንደሚገ፟ባ፟፡ትመላለሱ፡ዘንድ፡እንለምናለን።
13-14፤ርሱ፡ከጨለማ፡ሥልጣን፡አዳነን፥ቤዛነቱንም፡ርሱንም፡የኀጢአትን፡ስርየት፡ወዳገኘንበት፡ወደፍቅሩ፡ልጅ ፡መንግሥት፡አፈለሰን።
15-16፤ርሱም፡የማይታይ፡አምላክ፡ምሳሌ፡ነው።የሚታዩትና፡የማይታዩትም፥ዙፋናት፡ቢኾኑ፡ወይም፡ጌትነት፡ወይም ፡አለቅነት፡ወይም፡ሥልጣናት፥በሰማይና፡በምድር፡ያሉት፡ዅሉ፡በርሱ፡ተፈጥረዋልና፥ከፍጥረት፡ዅሉ፡በፊት፡በ ኵር፡ነው።ዅሉ፡በርሱና፡ለርሱ፡ተፈጥሯል።
17፤ርሱም፡ከዅሉ፡በፊት፡ነው፥ዅሉም፡በርሱ፡ተጋጥሟል።
18፤ርሱም፡የአካሉ፡ማለት፡የቤተ፡ክርስቲያን፡ራስ፡ነው።ርሱም፡በዅሉ፡ፊተኛ፡ይኾን፡ዘንድ፥መዠመሪያ፡ከሙታ ንም፡በኵር፡ነው።
19-20፤እግዚአብሔር፡ሙላቱ፡ዅሉ፡በርሱ፡እንዲኖር፥በርሱም፡በኩል፡በመስቀሉ፡ደም፡ሰላም፡አድርጎ፡በምድር፡ወ ይም፡በሰማያት፡ያሉትን፡ዅሉ፡ለራሱ፡እንዲያስታርቅ፡ፈቅዷልና።
21-22፤እናንተንም፡ነውርና፡ነቀፋ፡የሌላችኹና፡ቅዱሳን፡አድርጎ፡በርሱ፡ፊት፡ያቀርባችኹ፡ዘንድ፥በፊት፡የተለ ያችኹትን፡ክፉ፡ሥራችኹንም፡በማድረግ፡በዐሳባችኹ፡ጠላቶች፡የነበራችኹትን፡አኹን፡በሥጋው፡ሰውነት፡በሞቱ፡ በኩል፡አስታረቃችኹ።
23፤ይህም፥ተመሥርታችኹና፡ተደላድላችኹ፡ከሰማችኹትም፡ከወንጌል፡ተስፋ፡ሳትናወጡ፥በሃይማኖት፡ጸንታችኹ፡ብ ትኖሩ፡ይኾናል።ያም፡ወንጌል፡ከሰማይ፡በታች፡ባለው፡ፍጥረት፡ዅሉ፡ዘንድ፡የተሰበከ፡ነው፥እኔም፡ጳውሎስ፡የ ርሱ፡አገልጋይ፡ኾንኹ።
24፤አኹን፡በመከራዬ፡ስለ፡እናንተ፡ደስ፡ይለኛል፥ስለ፡አካሉም፡ማለት፡ስለ፡ቤተ፡ክርስቲያን፡በሥጋዬ፡በክር ስቶስ፡መከራ፡የጐደለውን፡እፈጽማለኹ።
25፤ስለ፡እናንተ፡እንደተሰጠኝ፡እንደእግዚአብሔር፡መጋቢነት፥የእግዚአብሔርን፡ቃል፡ፈጽሜ፡እንድሰብክ፡እኔ ፡የቤተ፡ክርስቲያን፡አገልጋይ፡ኾንኹ።
26፤ይህም፡ቃል፡ከዘለዓለምና፡ከትውልዶች፡ዠምሮ፡ተሰውሮ፡የነበረ፡ምስጢር፡ነው፥አኹን፡ግን፡ለቅዱሳኑ፡ተገ ልጧል።
27፤ለእነርሱም፡እግዚአብሔር፡በአሕዛብ፡ዘንድ፡ያለው፡የዚህ፡ምስጢር፡ክብር፡ባለጠግነት፡ምን፡እንደ፡ኾነ፡ ሊያስታውቅ፡ወደደ፥ምስጢሩም፡የክብር፡ተስፋ፡ያለው፡ክርስቶስ፡በእናንተ፡ዘንድ፡መኾኑ፡ነው።
28፤እኛም፡በክርስቶስ፡ፍጹም፡የሚኾን፡ሰውን፡ዅሉ፡እናቀርብ፡ዘንድ፡ሰውን፡ዅሉ፡እየገሠጽን፡ሰውንም፡ዅሉ፡ በጥበብ፡ዅሉ፡እያስተማርን፡የምንሰብከው፡ርሱ፡ነው።
29፤ለዚህም፡ነገር፡ደግሞ፥በእኔ፡በኀይል፡እንደሚሠራ፡እንደ፡አሠራሩ፡እየተጋደልኹ፥እደክማለኹ።
_______________ቆላስይስ፥ምዕራፍ፡2።______________
ምዕራፍ፡2፤
1፤ስለ፡እናንተና፡በሎዶቅያ፡ስላሉት፡ፊቴንም፡በሥጋ፡ስላላዩት፡ዅሉ፡እንዴት፡ያለ፡ትልቅ፡መጋደል፡እንዳለኝ ፡ልታውቁ፡እወዳለኹና።
2፤ልባቸው፡እንዲጸናና፥በፍቅርም፡ተባብረው፡በማስተዋል፡ወደሚገኝበት፡ወደመረዳት፡ባለጠግነት፡ዅሉ፡እንዲደ ርሱ፡የእግዚአብሔርንም፡ምስጢር፡ርሱንም፡ክርስቶስን፡እንዲያውቁ፡እጋደላለኹ።
3፤የተሰወረ፡የጥበብና፡የዕውቀት፡መዝገብ፡ዅሉ፡በርሱ፡ነውና።
4፤ማንም፡በሚያባብል፡ቃል፡እንዳያስታችኹ፡ይህን፡እላለኹ።
5፤በሥጋ፡ምንም፡እንኳ፡ብርቅ፥በመንፈስ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ነኝና፥ሥርዐታችኹንም፡በክርስቶስም፡ያለውን፡የእም ነታችኹን፡ጽናት፡እያየኹ፡ደስ፡ይለኛል።
6፤እንግዲህ፡ጌታን፡ክርስቶስ፡ኢየሱስን፡እንደ፡ተቀበላችኹት፡በርሱ፡ተመላለሱ።
7፤ሥር፡ሰዳችኹ፡በርሱ፡ታነጹ፥እንደ፡ተማራችኹም፡በሃይማኖት፡ጽኑ፥ምስጋናም፡ይብዛላችኹ።
8፤እንደክርስቶስ፡ትምህርት፡ሳይኾን፥እንደ፡ሰው፡ወግና፡እንደ፡ዓለማዊ፡እንደ፡መዠመሪያ፡ትምህርት፡ባለ፡በ ፍልስፍና፡በከንቱም፡መታለል፡ማንም፡እንዳይማርካችኹ፡ተጠበቁ።
9፤በርሱ፡የመለኮት፡ሙላት፡ዅሉ፡በሰውነት፡ተገልጦ፡ይኖራልና።
10፤ለአለቅነትና፡ለሥልጣንም፡ዅሉ፡ራስ፡በኾነ፡በርሱ፡ኾናችኹ፡ተሞልታችዃል።
11፤የሥጋንም፡ሰውነት፡በመገፈፍ፥በክርስቶስ፡መገረዝ፥በእጅ፡ባልተደረገ፡መገረዝ፡በርሱ፡ኾናችኹ፡ደግሞ፡ተ ገረዛችኹ።
12፤በጥምቀትም፡ከርሱ፡ጋራ፡ተቀብራችኹ፥በጥምቀት፡ደግሞ፥ከሙታን፡ባስነሣው፡በእግዚአብሔር፡አሠራር፡በማመ ናችኹ፥ከርሱ፡ጋራ፡ተነሣችኹ።
13፤እናንተም፡በበደላችኹና፡ሥጋችኹን፡ባለመገረዝ፡ሙታን፡በኾናችኹ፡ጊዜ፥ከርሱ፡ጋራ፡ሕይወትን፡ሰጣችኹ።በ ደላችኹን፡ዅሉ፡ይቅር፡አላችኹ።
14፤በእኛ፡ላይ፡የነበረውን፡የሚቃወመንንም፡በትእዛዛት፡የተጻፈውን፡የዕዳ፡ጽሕፈት፡ደመሰሰው።ርሱንም፡በመ ስቀል፡ጠርቆ፡ከመንገድ፡አስወግዶታል።
15፤አለቅነትንና፡ሥልጣናትን፡ገፎ፥ድል፡በመንሣት፡በርሱ፡እያዞራቸው፡በግልጥ፡አሳያቸው።
16፤እንግዲህ፡በመብል፡ወይም፡በመጠጥ፡ወይም፡ስለ፡በዓል፡ወይም፡ስለወር፡መባቻ፡ወይም፡ስለ፡ሰንበት፡ማንም ፡አይፍረድባችኹ።
17፤እነዚህ፡ሊመጡ፡ያሉት፡ነገሮች፡ጥላ፡ናቸውና፥አካሉ፡ግን፡የክርስቶስ፡ነው።
18፤ትሕትናንና፡የመላእክትን፡አምልኮ፡እየወደደ፥ባላየውም፡ያለፈቃድ፡እየገባ፥በሥጋዊም፡አእምሮ፡በከንቱ፡ እየታበየ፡ማንም፡አይፍረድባችኹ።
19፤እንደዚህ፡ያለ፡ሰው፡ራስ፡ወደሚኾነው፡አይጠጋም፥ከርሱም፡አካል፡ዅሉ፡በዥማትና፡በማሰሪያ፡ምግብን፡እየ ተቀበለ፡እየተጋጠመም፥እግዚአብሔር፡በሚሰጠው፡ማደግ፡ያድጋል።
20-21፤ከዓለማዊ፡ከመዠመሪያ፡ትምህርት፡ርቃችኹ፡ከክርስቶስ፡ጋራ፡ከሞታችኹ፥
22፤እንደ፡ሰው፡ሥርዐትና፡ትምህርት።አትያዝ፥አትቅመስ፥አትንካ፡ለሚሉት፡ትእዛዛት፡በዓለም፡እንደምትኖሩ፡ ስለ፡ምን፡ትገዛላችኹ፧እነዚህ፡ዅሉ፡በመደረግ፡ሊጠፉ፡ተወስነዋልና።
23፤ይህ፡እንደ፡ገዛ፡ፈቃድኽ፡በማምለክና፡በትሕትና፡ሥጋንም፡በመጨቈን፡ጥበብ፡ያለው፡ይመስላል፥ነገር፡ግን ፥ሥጋ፡ያለልክ፡እንዳይጠግብ፡ለመከልከል፡ምንም፡አይጠቅምም።
_______________ቆላስይስ፥ምዕራፍ፡3።______________
ምዕራፍ፡3፤
1፤እንግዲህ፡ከክርስቶስ፡ጋራ፡ከተነሣችኹ፥ክርስቶስ፡በእግዚአብሔር፡ቀኝ፡ተቀምጦ፡ባለበት፡በላይ፡ያለውን፡ ሹ።
2፤በላይ፡ያለውን፡ዐስቡ፡እንጂ፡በምድር፡ያለውን፡አይደለም።
3፤ሞታችዃልና፥ሕይወታችኹም፡በእግዚአብሔር፡ከክርስቶስ፡ጋራ፡ተሰውሯልና።
4፤ሕይወታችኹ፡የኾነ፡ክርስቶስ፡በሚገለጥበት፡ጊዜ፥በዚያን፡ጊዜ፡እናንተ፡ደግሞ፡ከርሱ፡ጋራ፡በክብር፡ትገለ ጣላችኹ።
5፤እንግዲህ፡በምድር፡ያሉቱን፡ብልቶቻችኹን፡ግደሉ፥እነዚህም፡ዝሙትና፡ርኵሰት፡ፍትወትም፡ክፉ፡ምኞትም፡ጣዖ ትንም፡ማምለክ፡የኾነ፡መጐምዠት፡ነው።
6፤በእነዚህም፡ጠንቅ፡የእግዚአብሔር፡ቍጣ፡በማይታዘዙ፡ልጆች፡ላይ፡ይመጣል።
7፤እናንተም፡ደግሞ፡ትኖሩባቸው፡በነበራችኹ፡ጊዜ፥በፊት፡በእነዚህ፡ተመላለሳችኹ።
8፤አኹን፡ግን፡እናንተ፡ደግሞ፡ቍጣንና፡ንዴትን፡ክፋትንም፥ከአፋችኹም፡ስድብን፡የሚያሳፍርንም፡ንግግር፡እነ ዚህን፡ዅሉ፡አስወግዱ።
9፤ርስ፡በርሳችኹ፡ውሸት፡አትነጋገሩ፥አሮጌውን፡ሰው፡ከሥራው፡ጋራ፡ገፋ፟ችኹታልና፥
10፤የፈጠረውንም፡ምሳሌ፡እንዲመስል፡ዕውቀትን፡ለማግኘት፡የሚታደሰውን፡ዐዲሱን፡ሰው፡ለብሳችኹታል።
11፤በዚያም፡የግሪክ፡ሰው፡አይሁዳዊም፡የተገረዘም፡ያልተገረዘም፡አረማዊም፡እስኩቴስም፡ባሪያም፡ጨዋ፡ሰውም ፡መኾን፡አልተቻለም፥ነገር፡ግን፥ክርስቶስ፡ዅሉ፡ነው፥በዅሉም፡ነው።
12፤እንግዲህ፡እንደእግዚአብሔር፡ምርጦች፡ቅዱሳን፡ኾናችኹ፡የተወደዳችኹም፡ኾናችኹ፥ምሕረትን፥ርኅራኄን፥ቸ ርነትን፥ትሕትናን፥የዋህነትን፥ትዕግሥትን፡ልበሱ።
13፤ርስ፡በርሳችኹ፡ትዕግሥትን፡አድርጉ፥ማንም፡በባልንጀራው፡ላይ፡የሚነቅፈው፡ነገር፡ካለው፥ይቅር፡ተባባሉ ።ክርስቶስ፡ይቅር፡እንዳላችኹ፡እናንተ፡ደግሞ፡እንዲሁ፡አድርጉ።
14፤በእነዚህም፡ዅሉ፡ላይ፡የፍጻሜ፡ማሰሪያ፡የኾነውን፡ፍቅርን፡ልበሱት።
15፤ባንድ፡አካልም፡የተጠራችኹለት፡ደግሞ፡የክርስቶስ፡ሰላም፡በልባችኹ፡ይግዛ።የምታመሰግኑም፡ኹኑ።
16፤የእግዚአብሔር፡ቃል፡በሙላት፡ይኑርባችኹ።በጥበብ፡ዅሉ፡ርስ፡በርሳችኹ፡አስተምሩና፡ገሥጹ።በመዝሙርና፡ በዝማሬ፡በመንፈሳዊም፡ቅኔ፡በጸጋው፡በልባችኹ፡ለእግዚአብሔር፡ዘምሩ።
17፤እግዚአብሔር፡አብን፡በርሱ፡እያመሰገናችኹ፥በቃል፡ቢኾን፡ወይም፡በሥራ፡የምታደርጉትን፡ዅሉ፡በጌታ፡በኢ የሱስ፡ስም፡አድርጉት።
18፤ሚስቶች፡ሆይ፥በጌታ፡እንደሚገ፟ባ፟፡ለባሎቻችኹ፡ተገዙ።
19፤ባሎች፡ሆይ፥ሚስቶቻችኹን፡ውደዱ፡መራራም፡አትኹኑባቸው።
20፤ልጆች፡ሆይ፥ይህ፡ለጌታ፡ደስ፡የሚያሠኝ፡ነውና፥በዅሉ፡ለወላጆቻችኹ፡ታዘዙ።
21፤አባቶች፡ሆይ፥ልባቸው፡እንዳይዝል፡ልጆቻችኹን፡አታበሳጯቸው።
22፤ባሪያዎች፡ሆይ፥በቅን፡ልብ፡ጌታን፡እየፈራችኹ፡እንጂ፥ለሰው፡ደስ፡እንደምታሠኙ፡ለታይታ፡የምትገዙ፡ሳት ኾኑ፥በሥጋ፡ጌታዎቻችኹ፡ለኾኑ፡በዅሉ፡ታዘዙ።
23፤ለሰው፡ሳይኾን፡ለጌታ፡እንደምታደርጉ፥የምታደርጉትን፡ዅሉ፡በትጋት፡አድርጉት፥
24፤ከጌታ፡የርስትን፡ብድራት፡እንድትቀበሉ፡ታውቃላችኹና።የምታገለግሉት፡ጌታ፡ክርስቶስ፡ነውና።
25፤የሚበድልም፡የበደለውን፡በብድራት፡ይቀበላል፥ለሰው፡ፊትም፡አድልዎ፡የለም።
_______________ቆላስይስ፥ምዕራፍ፡4።______________
ምዕራፍ፡4፤
1፤ጌታዎች፡ሆይ፥እናንተ፡ደግሞ፡በሰማይ፡ጌታ፡እንዳላችኹ፡ታውቃላችኹና፡ለባሪያዎቻችኹ፡በጽድቅና፡በቅንነት ፡አድርጉላቸው።
2፤ከማመስገን፡ጋራ፡በጸሎት፡እየነቃችኹ፡ለርሱ፡ትጉ።
3፤በዚያን፡ጊዜም፡ስለ፡ርሱ፡ደግሞ፡የታሰርኹበትን፡የክርስቶስን፡ምስጢር፡እንድንነግር፡እግዚአብሔር፡የቃሉ ን፡ደጅ፡ይከፍትልን፡ዘንድ፡ስለ፡እኛ፡ደግሞ፡ጸልዩ።
4፤ልናገር፡እንደሚገ፟ባ፟ኝ፡ያኽል፡እገልጠው፡ዘንድ፡ጸልዩልኝ።
5፤ዘመኑን፡እየዋጃችኹ፥በውጭ፡ባሉቱ፡ዘንድ፡በጥበብ፡ተመላለሱ።
6፤ለያንዳንዱ፡እንዴት፡እንድትመልሱ፡እንደሚገ፟ባ፟ችኹ፡ታውቁ፡ዘንድ፡ንግግራችኹ፡ዅልጊዜ፥በጨው፡እንደ፡ተ ቀመመ፥በጸጋ፡ይኹን።
7፤የተወደደ፡ወንድምና፡የታመነ፡አገልጋይ፡በጌታም፡ዐብሮኝ፡ባሪያ፡የኾነ፡ቲኪቆስ፡ኑሮዬን፡ዅሉ፡ያስታውቃች ዃል።
8-9፤ወሬያችንን፡እንድታውቁና፡ልባችኹን፡እንዲያጽናና፥ከእናንተ፡ከኾነውና፡ከታመነው፡ከተወደደውም፡ወንድም ፡ከአናሲሞስ፡ጋራ፡ወደ፡እናንተ፡የምልከው፡ስለዚህ፡ምክንያት፡ነው።የዚህን፡ስፍራ፡ወሬ፡ዅሉ፡ያስታውቋችዃ ል።
10-11፤ከተገረዙት፡ወገን፡ያሉት፥ዐብሮ፡ከእኔ፡ጋራ፡የታሰረ፡አርስጥሮኮስ፡የበርናባስም፡የወንድሙ፡ልጅ፡ማር ቆስ፡ኢዮስጦስም፡የተባለ፡ኢያሱ፡ሰላምታ፡ያቀርቡላችዃል።ስለ፡ማርቆስ፦ወደ፡እናንተ፡ቢመጣ፥ተቀበሉት፡የሚ ል፡ትእዛዝ፡ተቀበላችኹ።በእግዚአብሔር፡መንግሥት፡ከእኔ፡ጋራ፡ዐብረው፡የሚሠሩት፡እነዚህ፡ብቻ፡ናቸው፥እኔ ንም፡አጽናንተውኛል።
12፤ከእናንተ፡የኾነ፡የክርስቶስ፡ባሪያ፡ኤጳፍራ፡ሰላምታ፡ያቀርብላችዃል።በእግዚአብሔር፡ፈቃድ፡ዅሉ፡ተረድ ታችኹና፡ፍጹማን፡ኾናችኹ፡እንድትቆሙ፥ዅልጊዜ፡ስለ፡እናንተ፡በጸሎቱ፡ይጋደላል።
13፤ስለ፡እናንተ፡በሎዶቅያም፡በኢያራ፡ከተማም፡ስላሉቱ፡እጅግ፡እንዲቀና፡እመሰክርለታለኹና።
14፤የተወደደው፡ባለመድኀኒቱ፡ሉቃስ፡ዴማስም፡ሰላምታ፡ያቀርቡላችዃል።
15፤በሎዶቅያ፡ላሉቱ፡ወንድሞችና፡ለንምፉን፡በቤቱም፡ላለች፡ቤተ፡ክርስቲያን፡ሰላምታ፡አቅርቡልን።
16፤ይህችም፡መልእክት፡በእናንተ፡ዘንድ፡ከተነበበች፡በዃላ፥በሎዶቅያ፡ሰዎች፡ማኅበር፡ደግሞ፡እንድትነበብ፡ አድርጉ።ከሎዶቅያም፡የምትገኘውን፡መልእክት፡እናንተ፡ደግሞ፡አንቡ፟።
17፤ለአክሪጳም፦በጌታ፡የተቀበልኸውን፡አገልግሎት፡እንድትፈጽሙው፡ተጠንቀቅ፡በሉልኝ።
18፤በገዛ፡እጄ፡የተጻፈ፡የእኔ፡የጳውሎስ፡ሰላምታ፡ይህ፡ነው።እስራቴን፡ዐስቡ።ጸጋ፡ከእናንተ፡ጋራ፡ይኹን፨

http://www.gzamargna.net